አማርኛ 1
በውኑ በውሃውና በመንፈሱ ዳግም ተወልዳችኋልን? [አዲስ የተከለሰ ዕትም]የዚህ መጽሐፍ ዋና ርዕሰ ጉዳይ “በውሃና በመንፈስ እንደገና መወለድ” ነው። በዚህ መጽሐፍ ዋና ርዕሰ ጉዳይ ላይ ኦሪጂናል ነው። በሌላ አባባል፣ ይህ መጽሐፍ እንደገና መወለድ ምን እንደሆነና በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት በውሃና በመንፈስ እንዴት እንደገና እንደምንወለድ በግልጽ ይነግረናል። ውሃው በዮርዳኖስ የኢየሱስን ጥምቀት ይወክላል እንዲሁም መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ሁሉም ኃጢአታችን ወደ ኢየሱስ የተላለፈው በመጥምቁ ዮሐንስ በተጠመቀ ጊዜ ነው። ዮሐንስ የሰው ዘር ሁሉ ተወካይና የሊቀ ካህኑ የአሮን ዘር ነበር። አሮን በኃጢአት የማስተስረያ ቀን እጆቹን በተለቀቀው ፍየል ራስ ላይ በመጫን የእስራኤላውያንን ዓመታዊ ኃጢአት ሁሉ ወደ እሱ አሳልፎ ሰጠ። ይህ መስዋዕት ሊመጣ ያለው የበጎ ነገር ጥላ ነው። የኢየሱስ ጥምቀት የእጅ መጫን ምልክት ነው። ኢየሱስ በዮርዳኖስ በእጅ መጫን መልክ ተጠመቀ። ስለዚህ በጥምቀቱ የዓለምን ኃጢአት ሁሉ ወሰደና ስለ ኃጢአቱ ለመክፈል ተሰቀለ። ነገር ግን አብዛኛዎቹ ክርስቲያኖች ኢየሱስ በዮርዳኖስ በመጥምቁ ዮሐንስ ለምን እንደተጠመቀ አያውቁም። የኢየሱስ ጥምቀት የዚህ መጽሐፍ ቁልፍ ቃልና የውሃና የመንፈስ ወንጌል የማይነጠል ክፍል ነው። በኢየሱስ ጥምቀትና በመስቀሉ በማመን ብቻ እንደገና መወለድ እንችላለን።